በብዝሃ ዘርፍ ኢኮኖሚ እመርታዊ ለውጥ በማምጣት የማህበረሰቡን ህይወት በተጨባጭ ሊቀይር በሚችል መልኩ በቁርጠኝነት መስራት ይገባል፦ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር)
በመደመር መንግሥት ዕይታ የዘርፎች እመርታ “በሚል ሀሳብ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የብልጽግና ፓርቲ ሁለተኛ ዙር የከፍተኛና መካከለኛ አመራር ስልጠና ለቀጣይ ተልዕኮ ዝግጁነት በመፍጠር በስኬት ተጠናቋል። በስልጠናው ማጠቃለያ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) እንዳሉት እንደ ሀገር በብዝሃ ዘርፍ ላይ እመርታዊ ለውጥ በማስመዝግብ የህዝብን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ በርካታ ተግባራት ተከናውነዋል። እስካሁን የተገኙ ውጤቶችን አስጠብቆ በማስፋት በመደመር መንግስት እይታ በብዝሃ ዘርፍ ኢኮኖሚ እመርታዊ ለውጥ በማምጣት የማህበረሰቡን ህይወት በተጨባጭ ሊቀይር በሚችል መልኩ መስራት ይገባል ብለዋል። አመራሩ ችግሮችን ለመሻገርና ዐቅሞቻችንን በአግባቡ ለመጠቀም አዳዲስ ምልከታዎችና ከፍ ባለ ምናብ በፈጠራ ፣በፍጥነትና ዝላይ እሳቤዎችን በቁርጠኝነት በመተግበር እመርታዊ ለውጥ ለማምጣት ትኩረት የሚሻው ጉዳይ እንደሆነ አሳስበዋል። የግብርና ምርታማነትን ለማሻሻል በሚረዱ አሠራሮች ላይ ትኩረት ማድረግ ያስፈልጋል ያሉት ርዕሰ መስተዳድሩ ኩታ ገጠም እርሻ፣ ያልለሙ መሬቶችን ማልማት ፣የምርጥ ዘርና ማዳበሪያ አጠቃቀም ማሳደግና ሜካናይዜሽን እርሻን በመጠቀም የቤተሰብ ብልጽግናን እና የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ በቁርጠኝነት መስራት ይጠበቃል ብለዋል። የግብርና ትራንስፎርሜሽን ውጤታማ ለማድረግ በአግሮፕሮሰሲንግ ፣በኮመርሻላይዜሽንና እሴት የሚጨምሩ አሰራሮቹን መተግበር ያስፈልጋል ያሉት ርዕሰመስተዳድሩ የገጠር ፣የኢንዱስትሪያላይዜሽንና የከተማ ሽግግርን ውጤታማ ማድረግ ዋነኛ ተግባር እንደሆነ አስገንዝበዋል። በሌማት ትሩፋት ፣በአረንጓዴ አሻራ በከተማና በገጠር ኮሪደር፣በመሶብ አገልግሎት እንዲሁም በፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ አገልግሎት በቅንጂታዊ አንድነት አሰራሮችን በማሳለጥ ተጨበጭ ለውጥ ለማስመዝገብ በጊዜ የለንም መንፈስ መስራት ይገባል ብለዋል። የጊዜ አጠቃቀምን በመግራት ከተለምዷዊ የሥራ ባህል ባሻገር ያመለጡንን ዕድሎች በቁጭት ለማካካስ በሚያስችል ደረጃ በመንቀሳቀስ ብልጽግናን ማረጋገጥ ተቀዳሚ ተግባር መሆን እንዳለበት አንስተዋል። ሁለንተናዊ ብልጽግናን ለማረጋገጥ ዘላቂነት ያለው አስተማማኝ ኢኮኖሚ ለመገንባት የበረታን ሁነን መገኘትን ጊዜው ይጠይቃል ነው ያሉት። አመራሮች በንድፈ ሀሳብ የወሰደቱት ስልጠና ተግባራዊ በማድረግ የህዝቡን ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ ታሪካዊ ኃላፊነታቸውን አጠናክረው እንዲወጡ አስገንዝበዋል ።

