የክልሉ መንግሥት ከከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ጋር በመቀናጀት ለሁለንተናዊ ለውጥ ይሰራል:- አቶ ፍቅሬ አማን
በከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ሠላማዊ የመማር፣ ማስተማር ስራ እንዲቀጥል በማድረግ ብቁ ዜጋን ለማፍራት ያለመ ከክልሉ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት አመራሮችና የባለድርሻ አካላት በቦንጋ ከተማ የውይይት መድረክ እያካሄደ ይገኛል። የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የመንግስት ዋና ተጠሪ አቶ ፍቅሬ አማን በውይይቱ ላይ ተገኝተው ባስተላለፉት መልዕክት በክልሉ እስካሁኑ ጉዞ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት አስተዋጽኦ የጎላ እንደነበርና ይህንን ግንኙነት አጠናክሮ ለማስቀጠል…

